በአፍሪካ ትልቁ የፋሽን ሳምንት ለስምንተኛ ጊዜ በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው

0
600

በፋሽን ሳምንቱ ከ30 አገራት የተውጣጡ ከ200 በላይ አምራቾች ይሳተፉበታል ተብሏል

ማክሰኞ ጥቅምት 22 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) መሴ ፍራንክፈርት ኤግዚቢሽን ከኢንዱስትሪ ሚንስቴርና ከኢትዮጵያ ጨርቃ ጨርቅና አልባሳት አምራቾች ማኅበር ጋር በመተባበር ስምንተኛውን የአፍሪካ ሶርሲንግ እና የፋሽን ሳምንት በአዲ አበባ ስካይላይት ሆቴል ከጥቅምት 25-28 እንሚያካሂድ አስታውቋል፡፡

ለመላው አፍሪካውያን አምራቾች ትስስር ይፈጥራል በተባለው በዚሁ መድረክ፤ ከ30 አገራት የተውጣጡ ከ200 በላይ አምራቾች ይሳተፉበታል ያሉት የኢንዱስትሪ ሚንስቴር ሚንስትር ዲኤታ ታረቀኝ ቡሉልታ፣ 39 አገር በቀል ኩባንያዎች በመድረኩ እንሚሳተፉ ገልጸዋል፡፡

ይህ የአፍሪካ ሶርሲንግ እና የፋሽን ሳምንት በዘርፉ የአፍካ ትልቁ መድረክ ነው ያሉት ታረቀኝ ከ6000 በላይ ዓለም ዓቀፍ ገዢዎችም ምርቶችን እንሚጎበኙ ተናግረዋል፡፡

በዚህ መድረክ ላይ በአልባሳት ምርት ላይ የተሰማሩ የአፍሪካ አገራት የጥጥ፣ የጨርቃ ጨርቅ፣ የአልባሳት፣ የቴክኖሎጂ፣ የቆዳ ውጤቶች፣ የቤት ማስጌጫዎች እንሁዲም የፋሽን ዲዛይኖቻቸውን ለእይታ እንደሚያቀርቡ ይጠበቃል፡፡

መልስ አስቀምጡ

Please enter your comment!
Please enter your name here